የልደታ ብስራተ ገብርኤል አካባቢ
+251918511710
የቅሬታ አስተያየት መስጫ
ዓርብ, ህዳር 14, 2016 ዓ.ም
መግቢያ
ስለ እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
የዜጎች የስምምነት ሰነድ
የደንበኞች አገልግሎት
የአገልግሎት ቅድመ ሁኔታዎች
አገልግሎቶች
ለመልካም አስተዳደር አስተያየት
የቅሬታ አስተያየት መስጫ
የአገልግሎት እርካታ አስተያየት መስጫ
ደንብና መመሪያዎች
አቅም ግንባታ
ማስታወቂያ
ለማንኛዉም ጥያቄዎ
የጽ/ቤቱን ሮቦት ይጠይቁ
ሚዲያ
ዜና | News
ዶክመንተሪ (ቲቪ)
Video News
መጽሄቶች | Magazines
የወረዳዉ ጽ/ቤቶች
ትምህርት ጽ/ቤት
የስራና ክህሎት ጽ/ቤት
ፋይናንስ ጽ/ቤት
ሴቶች ህጻናትና ማ/ጉ/ጽ/ቤት
ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት
ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት
ህብረተሰብ ተሳትፎና በ/ፈ/ጽ/ቤት
ህብረት ስራ ጽ/ቤት
ሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት
ንግድ ጽ/ቤት
ከተማ ግብርና ጽ/ቤት
ፅዳትና ከተማ ውበት ጽ/ቤት
ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት
ወጣትና ስፓርት ጽ/ቤት
ዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት
ይግቡ
መግቢያ
ስለ እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
የዜጎች የስምምነት ሰነድ
አገልግሎቶች
ተቋማዊ አደረጃጀት
ሚዲያ
ዜናዎች | News
መጽሄቶች | Magazine
Online TV
ጠቃሚ መረጃዎች
ደንብና መመሪያዎች
ብሮሸር
የደንበኞች የእርካታ ዳሰሳ ገጽ
Web APP
ወረዳዎች
ወረዳ 1
ወረዳ 2
ወረዳ 3
ወረዳ 4
ወረዳ 5
ወረዳ 6
ወረዳ 7
ወረዳ 8
ወረዳ 9
ወረዳ 10
ይግቡ
ዜና | Oduu | News
የእንኳን ደስ አላችሁ የምስራችና የክብር መግለጫ! ታሪክ ዳግም ተጽፏል፤ ስኬት በድጋሚ ወደ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ጎርፏል!!!
ሀምሌ 12, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ለተከታታይ ጊዜያት ያስመዘገበውን የላቀ እና አርአያነት ያለው አፈጻጸም በመቀጠል፣ በ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ደረጃን በመያዝ በከተማችን አዲስ አበባ ደምቆ ወጥቷል። በዚህም ታላቅ ስኬት ለ2ኛ ጊዜ ተከታታይ የመኪና ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል! ይህ ስኬት ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን የዕለት ተዕለት የትጋት፣ የቁርጠኝነት እና የህብረት ውጤት ነው። ለአንጸባራቂው ስኬት ባለቤቶች የላቀ ምስጋና ይህ ታሪካዊ ድል እንዲመዘገብ ሌሊትና ቀን ሳይታክቱ ለደከሙት፦ ለተከበሩ የወረዳው ነዋሪዎች፡ ለልማትና ለለውጥ ሁልጊዜም ከጎናችን በመሆን ለምታሳዩት ቀጣይነት ያለው ድጋፍ እና ንቁ ተሳትፎ፣ ለላቀው አመራርና ቁርጠኛ ሰራተኞች፡ ህዝብን በታማኝነት፣ በቅልጥፍና እና በከፍተኛ ተነሳሽነት በማገልገል ለምታሳዩት ድንቅ የስራ ባህል፣ ለባለድርሻ አካላት፡ በየደረጃው ከጎናችን በመቆም ለምታደርጉት ሁለንተናዊ ድጋፍ፣ ልባዊ እና የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን! ይህ ድል የእናንተ የጋራ የድካም ፍሬ ነው! በከተማችን ከንቲባ የተበረከተ የክብር ምስጋና ሽልማት አመራሩና ሰራተኛው ይበልጥ እንዲነቃቃ፣ የውድድር መንፈስ እንዲሰፍን እና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እንዲሻሻል የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎች ይህንን የመሰለ ታላቅ ማበረታቻ ሽልማት ለሚያበረክቱት ለተከበሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ስራዎቻቸውን በማድነቅ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ይህ እውቅና ነገ ከዛሬ ይበልጥ ጠንክረን እንድንሰራ ትልቅ ጉልበት ይሆነናል። የወደፊት ራእያችን ወረዳ 8 ሁልጊዜም የስኬት እና የልማት ተምሳሌት ሆኖ ይቀጥላል። ይህ የ2ኛ ጊዜ የመኪና ሽልማት የመጨረሻችን ሳይሆን፣ ወደ ላቀ የህዝብ አገልግሎት እና የከተማችንን ብልጽግና ወደ ማረጋገጥ የምናደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን የነዳጅ ያህል ነው። የጋራ ስራ፣ የጋራ ስኬት! እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን! አቶ ደረጄ ፈይሳ የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ዋና ሥራ አስፈፃሚ
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 አስተዳደር "ኑ ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የመንግስት ሰራተኞች በጊዶ ዋሻ ችግኝ ተክለዋል።
ሀምሌ 10, 2018
በእለቱም ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ ከክረምት በጎ ፍቃድ አንዱ የሆነዉ የችግኝ ተከላ ነዉ ችግኝ በመትከል ሁሉም አካላት አሻራ በማስቀመጥ የአረንጓዴን ልምላሜን በማሳደግ የሀገራችንን የአየር ንብረት ተስማሚ ማድረግ አለብን ብሏል። የወረዳ 08 ብልግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኢንጅነር ይትባረክ ብርሃነ በበኩላቸው ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን መንከባከብም አለብን የምንተክላቸዉን ችግኞች በጥንቃቄ በመትከል አሻራችንን ማሳረፍ አለብን ሲሉ ተናግረዋል።
ዜና | Oduu | News
ለመንግስት ሰራተኞች የሰዓት መቆጣጠሪያ የጣት አሻራ አፈፃፀም ዙሪያ ላይ ግንዛቤ ተሰጠ!
ሰኔ 27, 2018
የልደታ ክ/ከተማ የወረዳ 8 አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ሰራተኞች የሰዓት መቆጣጠሪያ የጣት አሻራ አፈፃፀም ዙሪያ ውይይት አካሂዷል። የወረዳ 08 ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አምባቸው ተፈራ የጣት አሻራ ያስፈለገበት ምክንያት በከተማ አስተዳደሩ በየደረጃው የሚገኙ ሁሉም ሰራተኞች በጣት አሻራ የሰዓት መቆጣጠሪያ ላይ ደረጃውን የጠበቀ፣ አስተማማኝ ፣ቀልጣፋ፣ተጠያቂነት እና ግልፅነት እንዲኖረው ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል ። አቶ አምባቸዉ አክለዉም የጣት አሻራ ከሀምሌ 01/2018 ዓ.ም እንደሚጀምር ተናግረዉ የመንግስት ሰራተኞች በዓመት ፍቃድ በወሊድ ፍቃድ በህመም እና በሌሎች በመስራያ ቤቱ በሚታወቁ ህጋዊ ፍቃዶች በስራ በማይገኙበት ጊዜ ለሰው ሃብት አስተዳደሩ ክፍል በሲስተሙ የቀረበበትን ምክንያት ማረጋገጥ አለበት ፤ሆኖም የታየዘው የጊዜ ገደብ ሲጠናቀቅ ወደ መደበኛ የአሻራ ቁጥጥር ስርዓት እንዲገባ ተናግረዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ የፋይናስ ጽ/ቤት የአይሲቲ ቡድን መሪ አቶ ሰለሞን ታደሰ ሁሉም የወረዳው ቋሚ ሰራተኞች ለአሻራ መስጠት እንዳለባቸው በመግለፅ ሁሉም ሰራተኛ የአተገባበር መመሪያው ተግባራዊ እንዲያደርግ አሳስበዋል:: በዉይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል ።
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ በወረዳ 08 የባለጉዳይ ቀን መሰረት በማድረግ የተቋማት አገልግሎት አሰጣጡ ከምንግዚውም የተሻለ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ተገልጋዮች ተናገሩ ።
ሰኔ 10, 2018
ተገልጋዮች እንደገለፁት ባለሙያዎች እና አመራሮች የባለጉዳይን ቀን ያለምንም እንግልት ለማገልገል በስራ ገበታቸዉ ላይ በመሆን ቀልጣፍ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በተደረገዉ ምልከታ ቀልጣፋ አገልግሎት የመስጠትና ተገልጋዩን ከእንግልት የፀዳ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ የማሳደግ የትኩረት አቅጣጫ መሆን እንዳለበት ያነጋገርናቸው ባለጉዳዮች ገልፀዋል ።
ዜና | Oduu | News
የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤን መቋቋሙ አገልግሎት አሰጣጡ ላይ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን ለመፍታት ላቀ ያለ ሚና እንዳለው ተገለፀ።
ታህሳስ 24, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ስርቪስና የሰው ሃብት አስተዳደር ጽ/ቤት በ6 ወር በመማክርት ጉባኤው የተከናወኑ ተግባራት ተገምግሟል። በመድረኩ ከክፍለ ከተማና ከወረዳ የተውጣጡ አስተባባሪዎች ፣ ቡድን መሪዎችና የመማክርት ጉባኤ ስራ አስፈፃሚዎች የተሳተፉ ሲሆን የክ/ከተማው ፐ/ሰ/የሰ/ሀ/ል/ጽ/ቤት የሪፎርም ክትትልና ድጋፍ ቡድን መሪ አቶ ሙሉጌታ ንጋቱ መማክርት ጉባኤ ያከናወናቸውን ተግባራት ሰነድ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል ። የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ስርቪስና የሰው ሀብት አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ መቅደስ ያደታ እንዳሉት በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት መማክርት ጉባኤው ተገልጋዩንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማቀናጀት ያሉ አቅሞችን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጡንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል አሰራር በመዘርጋ በርካታ ተግባራት መሰራታቸውን ገልጸዋል ። ለተገልጋዮች ፈጣንና ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ መማክርት ጉባኤው ያለው ሚና የጎላ ያሉት ወ/ሮ መቅደስ አያይው አገልግሎት አሰጣጡ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ መማክርት ጉባኤው ያለው ሚና የጎላ መሆኑን ገልፀዋል። የመድረኩ ከተሳታፊዎችም መማክርት ጉባኤ መቋቋሙ አገልግሎት አሰጣጡን ላይ የተሻለ ለውጥ እያመጣ እንደሆነ አንስተዋል።
መግቢያ
ስለ_እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
አገልግሎቶች
ተቋማዊ አደረጃጀት
ሚዲያ
ዜናዎች | News
ፎቶግራፎች | Photo Gallery
ቪዲዮዎች | Videos
መግለጫዎች | Press Release
መጽሄቶች | Magazine
ጠቃሚ መረጃዎች
ደንብና መመሪያዎች
ብሮሸር
የደንበኞች የእርካታ ዳሰሳ ገጽ
Online TV
Web APP
የዛሬይቱ ልደታ
ወረዳዎች
ወረዳ 1
ወረዳ 2
ወረዳ 3
ወረዳ 4
ወረዳ 5
ወረዳ 6
ወረዳ 7
ወረዳ 8
ወረዳ 9
ወረዳ 10
ያግኙን
lidetaw8public@gmail.com
+251918511710